tg-me.com/orthodoxzelalemawit/6655
Last Update:
ስብከታችን እኛን ራሳችንን መለወጥ ሳይችል ሌሎችን እንዲለውጥ መመኘት ሞኝነት ነው። መጽሐፋችን በእኛ ላይ መልካም ለውጥን ካላመጣ ሌላው ገዝቶ እንዲያነበው ማስተዋወቅ ከንቱ ድካም ነው። ስብከታችን፣ መጽሐፋችን መጀመሪያ መለወጥ ያለበት እኛን ራሳችንን ነው።
አንድ መጽሐፍ ወይም ስብከት ከሚከተሉት ነገሮች ቢያንስ በአንዱ ሊጠቅመኝ ይገባል።
❤ ጥሩ ስነ ምግባር እንዲኖረኝ ማድረግ
❤ የክህሎት እድገት እንዲኖረኝ ማድረግ
❤ ሃይማኖታዊ ዕውቀት እንዲኖረኝ ማድረግ
❤ ከክፉ ሥራዎች ማራቅ
❤ የሕይወትን መንገድ ማሳየት
❤ መልካምን እንዳስብ ማድረግ
አለበት። እኛ ስድብን ሳንተው ሌላው ሰድብን እንዲተው መስበክ አስቂኝ ነው። እኛ መኖር ያቃተንን ሕይወት ሌሎች እንዲኖሩት አብዝቶ መናገር ከንቱነት ነው። ሌሎች የእኛን ቃል ሰምተው ሊለወጡበት ይችላሉ። እኛ ግን እንደ ገንዳ ሆነን እንቀራለን። የክርስትና ሕይወት በልብ የሚያስቡት፥ በቃል የሚናገሩት፣ በተግባር የሚያሳዩት ሕይወት ነው።
በመንፈሳዊ ሕይወታችን ለማደግ እናንብብ፣ እንማር፣ እንጠይቅ።
© በትረ ማርያም አበባው
BY አንዲት እምነት ✟✟✟
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/orthodoxzelalemawit/6655